Wednesday, November 9, 2011

ትዕግሥት


ት የውን ቃል ወይም ጽንሰ ሃሳብ በአብዛኛው የመንጠቀምበት ስሜታችን የሚፈታተኑ ነገሮችን ችሎ ከማለፍ ጋር በተያያዘ ነው። ለዚህም በተለምዶ

“መቻል ምን ይከፋል
ሆድ ከአገር ይሰፋል” ይባላል።

አንድን ነገር ታግሠን በማሳለፋችንም በአብዛኛው ደስተኞች እንሆናለን። ይህ አይነቱ መታገሥ በወቅቱ የባሰ ችግር እንዳይገጥም የሚጠቅም ሲሆን በችግሩ ዙሪያ ግን ዘለቄታዊ መፍትሄ ላያመጣ ይችላል። ት ስሜትን አምቆ መያዝ ሳይሆን የምንፈልገው ነገር ቀና በሆነ አስተሳሰብ ይሆናል ብሎ መጠበቅን ይመለከታል። ት ውጤቱ ብቻ ሳይሆን በትክክል ከታገን ሂደቱም አስደሳች ነው። በውስጥ “አንጀትን እያሳረሩ” ስለትት ማውራት ትዕግሥትን በሚገባ አለመረዳትን ከማመላከቱም በላይ ጎጂነቱ ስለሚያመዝን ሰዎች መታገስን እንደሞኝነት ሊቆጥሩት
ትዕግሥት ምንድን ነው?
በህይዎታችን መታገን የሚፈልጉ ብዙ ገጠመኞች አሉ። በዚህ ውስብስብ በሆነ ዓለም ውስጥ መታገሥ ወይም አለመታገሥ ጉልህ አስተዋጽኦ አላቸው። አንዳንዴ ት ሳይሆን ፍጥነት የሚያስፈልጋቸው ነገሮች አሉ። የአንድ ደቂቃ መዘግየት ይኸ ነው የማይባል የሕይዎት ዘመን ዕድል ሊያሳጣ ይችላል። በተቃራኒው ደግሞ ለሴኮንዶች መታገሥ አለመቻል ለህልፈተ ሕይዎት ያደርሳል። ለምሳሌ ያህል መኪና የሚነዳ ሰው መታገሥ ባለመቻሉ ከፍተኛ አደጋ እንዲደርስ ያደርጋል። ይህ እንግዲህ ን ከጊዜ ጋር ስናየው የመታገሡ ሁኔታ ሳይሆን ጊዜ ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ ነው የምናየው። በአንድበኩል በመዘግየት ሊቀርብን የሚችል አጋጣሚ በሌላ በኩል ደግሞ በመቸኮል የሚደርስብን ጉዳት። የተረጋጋ ሕይዎት ያለው በብርሃን የሚኖር ይህንን መለየት ስለማይቸገር ሁለቱንም እንደሁኔታቸው ያከናውናል።
ይህንን ጽንሰ ሐሳብ ማለትም ከጊዜ ጋር የተያያዘውን ያመጣሁበት ምክንያት አንባቢዎቼ “መታገሥ ድርጊት አለመፈጸም ነው” ከሚለው ጋር እንዳያያይዙት ከመፈለግ ነው። እየሱስ ክርስቶስ ያንን ሁሉ መከራ በ ያሳለፈበት ምክንያት ውጤቱን በማወቁ ነው። ውጤቱም ለሰው ልጆች ድኅነትን ማምጣት፣ የእግዚአብሔርን ማንነት ማሳየት - ሙቶ ሌሎችን በማዳን። እንደዚህ አይነቱ ከፍተኛ ኃይል አለው። መታገሥ የሚያስፈልጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ። ለምሳሌ ያህል፦
·         የቤተሰብ ግንኙነት የሰመረ ለመሆን
·         በሥራ ቦታ ከሥራ ባልደረቦች ጋር ያለ ግንኙነት አለማማር
·         ያለንበት የኢኮኖሚ ሁኔታ ዝቅተኝነት
·         በራሳችንም ሆነ  በምንወዳቸው ላይ የደረሰ የጤና ችግር
·         የምንወዳቸው ሰዎች ያሉበት ሁኔታ መልካም አለመሆንና የመሳሰሉት
·         በዓለም ላይ ያሉ ፍትሀዊ ያልሆኑ አሰራሮች
ባለት ዘመን የሚታዩ ክስተቶች ናቸው። እነዚህ ክስተቶችም እልህ አስጨራሾችና ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ይታመናል። ሰዎች የችግራቸውን መፍትሔ የማግኛ ጊዜ ለማሳጠር መታገስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይህንን ስል የችግሩ ባለቤቶች እጃቸውንና እግራቸውን አጣጥፈው ቁጭ ይላሉ ማለት አይደለም። ማድረግ ያለባቸውን ነገር መጫዎት ያለባቸውን ጨዋታ ማለትም የራሳቸውን ድርሻ መወጣት የግድ ነው። መታገስ ማለትም ውጤቱን ከመጠበቅ አንጻር እንጂ የራስን ድርሻ ለመፈጸም መታገስ ቦታ የለውም።
አንዳንድ ጊዜ ችግር ሲደርስ ከችግሩ በመሸሽ መፍትሔ ያገኘን ሊመስለን ይችላል። ሆኖም ግን ዘለቄታዊ መፍትሔ የምናገኘው ችግሩን በመግጠም ነው። ችግሩ በደረሰ ጊዜም ከችግሩ መሸሽ ሳይሆን በ መፍትሔ መፈለግ ጠቃሚ ነው። ጠቢቡ ሰለሞን የን ኃይል ሲገልጽትዕግሥት ታላቁን ኃጢአት ጸጥ ያደርጋልና የገዢ ቍጣ የተነሣብህ እንደ ሆነ ስፍራህን አትልቀቅ። (መክብብ 10:4) በበላይ አካል ቁጣ ተደናግጦ ቦታን መልቀቅ እንደማያስፈልግና በኃጢአት ላይ ምን ያህል ሃያል ስልጣን እንዳለው ያስረዳናል። ቦታውን ከለቀቅን የምናስበውን ነገር ተተነዋልና ሊደግፉን የሚያስቡ ሰዎች ካሉም ሀሳባችን መተዋችንን (መሸሻችንን) በማየት ሊዘረጉ ያሰቡትን የትብብር እጅ ይሰበስባሉ።
ከት ጋር ሁልጊዜ አብሮ የሚሄደው ቀና አስተሰሰብ ነው። ስንታገሥ ውጤቱ መልካም ይሆናል በሚል አስተሳሰብና ለቀናው ነገር መምጣት የበኩላችን አስተዋጽኦ በማድረግ መሆን አለበት። ጠማማው ይቃናል፣ የጎደለው ይሞላል፣ የተጣላው ይታረቃል፣ የታመመው ይድናል፣ የወደቀው ይነሳል፣ የተጣላው ይታረቃል፣ ያበላሸው ያስተካክላል፣ ያልታየው ያያል፣ የተደበቀው ይገለጻል፣ የጠፋው ይገኛል፣ ያጣው ያገኛል፣ የተሳሳተው ይመለሳል እና የመሳሰሉትን ቀና አስተሳሰቦች በማሰብና ለተግባራዊነታቸውም ሌት ተቀን መሥራትን ይፈልጋል። ትዕግሥት እንቅስቃሴ አልባ ሳይሆን በይሁንታዊ ቀና አስተሳሰብ እየተመራ ተግባራዊ እንቅስቃሴን ይፈልጋል።   
በቅዱስ መጽሐፍ እንደምናየው ነቢያት ከፍተኛ ችግር የደረሰባቸው ቢሆንም የሚጠብቁትን ነገር ይሆናል ብለው አምነው ይህንኑም በትዕግሥት ጠብቀዋል። ይህንንም ያዕቆብ ሲገልጽ እንዲህ ይላል “ወንድሞች ሆይ፥ የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ።” (ያዕቆብ 5:10) በያዕቆብ መልዕክት ምዕራፍ 1:2-4 እንደተጠቀሰው በእምነታችን ላይ ለሚመጣው ፈተና ትዕግሥት ሥራውን እንዲሠራ ሁኔታውም ሲከሰት ደስ ሊለን እንደሚገባ ያስረዳል። ፈተና በቀና ለሚመለከቱትና ለተዘጋጁ ተማሪዎች ከክፍል ወደ ክፍል እንደሚያሳልፍ ሁሉ በሕይዎትም የሚገጥም ችግር ወደተሻለ ደረጃ እንደሚያሸጋግር እሙን ነው። የፈጠራ ሥራዎች የችግር መፍትሄዎች ናቸው። “ችግር ብልሀትን ይፈጥራል” እንደሚባለው።   
መከራን በመታገስ ዋነኛ ስፍራ ከሚይዙት ውስጥ ኢዮብ አንዱና ታላቁ ነው። ኢዮብም መታገሱን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርም እንደፈጸመለትም መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል። “እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደ ፈጸመለት አይታችኋል፤ ጌታ እጅግ የሚምር የሚራራም ነውና።” (ያዕቆብ 5:11) የእግዚአብሔር ለሚታገሡት ምህረቱ እምን ነው።
ብዙ ፈታኝ ነገሮች በሩቅም ተፈጽመው ተመዝግበው ያሉም ሆነ አሁን በቅርብ ዘመን የተከሰቱት ትዕግሥትን የጠየቁ ነገሮች በአብዛኛው ረጂም ጊዜን ወስደዋል። እስራኤላውያን በነቢዩ ሙሴ እየተመሩ ከግብጽ ወጥተው ወደ ቃል ኪዳን መሬት ሲሄዱ ጉዞው እልህ አስጨራሽ ከመሆኑም በላይ ብዙ ዓመታትን (40 ዓመታት) ወስዷል። ብዙዎችም ወገኖቻቸው እንደሚደርሱ ከማመን በስተቀር ባይናቸው ለማየት አልበቁም። ተመሳሳይነት ያላቸው ከዚያ ቀረብ ያሉ ብዙ ክስተቶችንም መጥቀስ ይቻላል። ይህንንም ለአንባቢዎቸ እተወዋለሁ።
በእግዚአብሔር ለሚያምኑና መንፈሳውያን ለሆኑ ሕይዎታቸውን ለጌታ ለእየሱስ ክርስቶስ ለሰጡ የመንፈስን ፍሬዎች ማፍራት እንዳለብን ሐዋርያው ጳውሎስ ሲያስተምረን ፍሬዎች ብሎ ከገለጻቸው ውስጥ “ትዕግሥት” አንዱ ነው።  እግዚአብሔርም ለሰው ልጆች በአካል የተገለጸ ባይሆንም መልካም እንደሚያስብ በነቢዩ ኤርሚያስ “ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።” (ኤር 29:11) ሲል ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል። መልካሙንም ነገር ሁሉ በጊዜው ያደርጋል ብሎ በእምነትና በትዕግሥት መጠበቅ መንፈሳዊ ፍሬ የማፍራት ምልክት ነው። 

... በሚቀጥለው ትዕግሥት ለምን ያስፈልጋል? እና የሚፈታተነንን ወይም ጊዜ የሚውስድን  ነገር እንዴት ልንታገእንችላለን? በሚሉት ጉዳዮች ላይ ያለኝን ሐሳብ አቀርባለሁ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ነጋ ዓለማየሁ

No comments:

Post a Comment