Wednesday, March 20, 2019

ኃላፊነት

ኃላፊነት

የሰው ልጅ ማንም ከማንም ሳይበልጥ እና ሳያንስ እኩል ስጦታ ይሰጠዋል። ስጦታውም የጊዜ ስጦታ ነው። ለምሳሌ ያህል ሁሉም ጧት ሲነሳ እኩል 24 ሰዓታት ይሰጠዋል። አንዱ ብዙ ሥራ አለበትና ብዙ ሰዓታት ያስፈልገዋል አይባልም። በሌላ በኩልም እከሌ ብዙ ሥራ ስለሌለው ሰዓት የቀነስበት አይባልም። ሁላችንም እኩል 24 ሰዓታት ይሰጠናል። የተሰጠነን 24 ሰዓታት አጠቃቀማችን ልዩነትን ይፈጥራል። አንዳንዱ በኃላፊነት ስሜት እያንዳንዷን ደቂቃ ይጠቀምባታል፣ በተገቢ ሁኔታም ያሳልፋታል። አንዳንዱ ደግሞ ደቂቃዎች አይደሉም ሰዓታት እንደ አልባሌ ይባክናሉ። ለእራስ ከመባከናቸውም ባሻገር ለሌሎችም መልካም ያልሆነ ግብአት የሚሆን ነገር ሊተገብሩ ይችላሉ።

ማንኛውም ክንዋኔ መሠረቱ ወይም ዘሩ ሐሳብ ነው። ከ24 ሰዓታት ውስጥ ለማሰብ የሚዉሉ አሉ ፣ ለመናገር ወይም ለመጻፍ የሚዉሉ አሉ፣ ለተግባራዊ ክንዋኔም የሚዉሉ አሉ። ከሐሳብ ጀምሮ ያለው ነገር ጉልበት ነውና በጥንቃቄ ሊያዝ ይገባል። ሐሳብ ጉልበት (Energy) ነው። ሐሳብ በምናስብበት ጊዜ ጉልበት እየላክን ነው። የጉልበቱ መጠን የሚለካው በሐሳቡ ጥንካሪ ነው። ጠንካራ ፍላጎት ባለው ሰው የታሰበ ሐሳብ ከፍተኛ ጉልበት አለውና በቀላሉ ወደተግባር የተረጎማል። ታዲያ ይህን የተገነዘቡ ሰዎች ስለሚያስቡት ነገር ይጠነቀቃሉ። ለምን ቢባል ተግባራዊ ይሆናልና። ስለዚህ ሰዎች በአካል ስለሚያከናውኑት ተግባር ብቻ ሳይሆን በአእምሯቸው ስለሚያስቡት ሐሳብም ጥንቃቄና ኃላፊነት ይወስዳሉ። ለምን ቢባል ማን እንደሚቀበለውና ተግባራዊ እንደሚያደርገው አይታወቅም። ስለሆነም ሰለእራሳችንም ሆነ ስለቤተሰብ ከዚያም ከፍ ብ ሎ ስለማህበረሰብና አገር የምናስበውን ነገር ጥ ንቃቄ ልናደርግበት ይገባል። መልካም ያልሆነን ሐሳብ መተው እንጂ መያዝ አያስፈልግም። ጉልበት ነውና አንዱ ሊጠቀምበት ይችላል። ስለዚህ ይህን ተገንዝበን ኃላፊነት እንውሰድ። መልካም መልካሙን እንስብ፣ መልካሙን እንናገር፣ መልካሙን እንተግብር። የሐሳብም፣ የቃላትም ሆነ ሆነ የተግባር ተመጣጣኝ ምላሽ ወደ ባለቤቱ ይመለሳልና መልካሙን በጥንቃቄ እንምረጥ።

ነጋ ዓለማየሁ
3/20/2019

Thursday, February 7, 2013

ሲያቀብጠኝ ነው ወይስ ሲፈትነኝ?


ሲያቀብጠኝ ነው ወይስ ሲፈትነኝ

ሲያቀብጠኝ ነው ወይስ ሲፈትነኝ፣
እዚያ ወስዶ የከተተኝ።
እያልኩ እራሴን ብጠይቅ፣
መልስ ለማግኜት ብጨነቅ።
ፈተና ነው እለፈው፣
ሲያስፈልግም ተወው።
ይለኛል የእራሴ ድምጽ፣
ሳያሰማ ምንም አመጽ።
መጀመሪያ ሲመርጡኝ፣
ለምነው ነበር ያስገቡኝ።
እምቢ ብትል ብትሸሽ እንደ ዮናስ፣
ጥሪህን አልቀበል ብለህ የኃያሉን ንጉሥ፣
መሄጃም የለህ ማምለጫ የትም አትደርስ።
ብለው ወንድሞች ሲነግሩኝና ሲማጸኑኝ፣
እኔም እሺ ብየ እያቅማማሁ ገባሁኝ።  
እኔም አንድ ሐጢያተኛ።
ያለስህተት የማልተኛ።
አምላኬን የምበድል በጧት በማታ።
ምስጋና ቅዳሴ የማጎድል እንዲሁም እልልታ።
ይህንንስ አውቃለሁ፣
ነጋሪም አልፈልግም ሁልጊዜ አለቅሳለሁ።
አስታዋሺም አልሻ፣
አምላኬም ያውቃል እንዳለብኝ የመንፈስ ልምሻ።
ስለእኔ ችግር መናገር ምን ሊጠቅም፣
ከእዳ ነጻ አያወጣ ከድካም አያገግም።
አምላክ እንደሆን ከእነ ድክመቴ ያውቀኛል፣
ተገርፎም በመስቀል ላይ ሞቶልኛል፣
ከሞትም አድኖኛል።
ነጋ ሲሉ አልነጋም አኩኩሉ ጨዋታ።
እንጫወት ለአፍታ፣
ይላል ሥራ ሊያስፈታ።
ሰዓቱ የማን ሆኖ የምንጫዎትበት፣
አይጠቅምም ብናቀርበው ለአምላካችን መስዋዕት።
እያንዳንዷ ጊዜ ከሳሹ ያጠፋት፣
ለመልካም ሳይሆን ለክፋት፤
ባለቤቱን ያሳዝናል፣
ለኪሳራም ይዳርጋል።
መስሏቸው ነበር የምንተወው ክሱ አሰልችቶን፣
አምላክ ግን በጥበቡ ለእኛ ጉልበትን ሰጥቶን፤
ይኸውና እንሰራለን ለበረከት እንደክማለን፤
እኔ ግን እላለሁ ለከሳሹም እንጸልይ፣
አብረን ነውና ያለነው በምድር አይደለም በሰማይ።
እሳት ቢነሳ በጎረቤት፣
ይደርሳልና ከቤት።
አብሮ ማጥፋት ነው ተባብሮ፣
ያለውን መሰናክል ሰብሮ።
ካልሆነ ያወድመናል፣
ሁላችንም ይበላናል፤
ታዲያ ጎበዝ አይዞን እንበል
ሞት እንደሆን አይቀርም
ስም ግን አይቀበርም፤
መልካም ሠርቶ  ማለፍን፣
ለመጪው ትውልድ መተካትን፣
እንወቅበት ሁላችን፣
እንድንሄድ ወደ አገራችን።
አገራችን የት ነው ለሚሉ፣
መሠረታዊውን ላላሟሉ።
ነግሮናል መምህራችን፣
ጳውሎስ ሐዋርያው አባታችን።
አገራችን በሰማይ ነው፣
ዜግነታችንም እዛው ነው።
እያለ የሰበከልን፣
የጌታን ወንጌል ያስተማረን።
ያመላከተን መንገዱን፣
ጌታ የተለመውን።

                        ነጋ ዓለማየሁ (12/16/2012)  

Monday, November 21, 2011

ራስን መግዛት

አንድ  ትልቅ ሰው ነበሩ አሉ። እኚህ ሰው በስተመጨረሻ  ዘመናቸው አንድ ትልቅ ነገር ተገለጠላቸውና ለሌላው ትምህርት ይሆን ዘንድ ታሪካቸውን ተናገሩ። ነገሩ እንዲህ ነው። ሰውየው በልጅነት ዘመናቸው በጣም ታላቅ ነገር ያስባሉ። ይኸውም ዓለምን መቀየር ነበር። በመሆኑም ዓለምን መቀየር አለብኝ ብለው ተነሱ። ከዚያም ውለው አድረው ሲመለከቱት ዓለም በጣም ትልቅ በመሆኑ አገሬን ብቀይር መልካም ነው ብለው ተነሱ። ከዚያም ውለው አድረው ሲያስቡት አገር ትልቅ ነው። ስለዚህ ያለሁበት ክፍለ ግዛት መቀየር አለብኝ አሉ። ከዚያም ይህም አደከማቸውና ያለሁበትን አካባቢ ብቀይር ይሻላል አሉ። ይህ ሁሉ ሲሆን እድሜ  እየጨመረ ቤተሰብም ተመስርቶ ከእውነታውም እየተማሩ ነው። በኋላም ይህ ሁሉ አይቻልም የራሴን ቤተሰብ ብቻ ብቀይር ትልቅ ነገር አደረኩ ማለት ነው ብለው ቤተሰባቸውን ለመቀየር ቆርጠው ተነሱ። የሚገርመው ነገር ያም አልሆን አለና ብዙ ሙከራ አድርገው ጊዜው ካለፈ በኋላ በስተመጨረሻ ብልጭ ያላበቸው ነገር “መለወጥ የምችለው ራሴን ብቻ ነው” አሉ። “ይንን ቀደም ብዬ ባውቅ ኑሮ  እውነትም ሌሎችንም ላነሳሳ አርአያም ልሆናቸው እችል ነበር። እኔ ስለወጥ ዓለምም ይለወጣል” ብለው ደመደሙ። 

ራስን መግዛት ቀላል ነገር አይደለም። በዘመናችን ራሳችን መግዛት አቅቶን ሌሎችን ግን ለመግዛት ብዙ እንጥራለን። ያ ባለመሆኑም ስንናደድ በራሳችን ጤና  ላይ ችግር ስንፈጥር እንገኛለን። ራሱን በሚገባ  የገዛ ሰው በሌሎች ላይ ለመንገሥ ብዙ ችግር የለበትም። በምሳሌነት መምራት ማለትም ይኸው ነው። የስሜት ሕዋሳቶች የሚያመጡትን ነገር ያለምንም ማጣራት ከተጠቀምንባቸው የስሜት ተገዢ እንጂ ስሜታችን የገዛን ወይም በራሳችን ላይ የነገሥን አይደለንም። ለምሳሌ ብንወስድ ዓይን የውጪውን ነገር ያያል፣ በማየቱም አእምሮአችንም  ቀደም ሲል ከነበረው መረጃ  ጋር ያገናዝብና ወደ አንድ ነገር ወደ ማድረግ ፍላጎት ይሄዳል። በዚያ  ወቅት ራስን መግዛት የተላበሰ ሰው ዓይንን እንደ ሠራተኛ (Subject) በመቁጠር እንጂ እንደ ውሳኔ ሰጪ ባለመቁጠር ሕሊና የሚለውን ማድረግ ይችላል። እንዲሁም ሌሎች የስሜት ሕዋሳቶች የሚያመጡትን የፍላጎት ምንጭ የሚሆኑትን መረጃዎች እንደ አስፈላጊነቱ እየተጠቀመ ራስን በመግዛት አኳኋን ውሳኔ  ይሰጣል። ንጉሡ ሕሊና ይሆናል ማለት ነው። የስሜት ሕዋሳትም ለንጉሡ የሚያገለግሉ ሚኒስትሮች ይሆናሉ።      

ራሱን የሚገዛ ሰው አፍንጫ ያሸተተውን፣ ጀሮ የሰማውን፣ ዓይን ያየውን፣ ጣትም የዳሰሰውን፣ ምላስም የቀመሰውን ወይም አእምሮ ያሰበውን ሁሉ አያደርግም። እነዚህን የሥራ ክፍሎች በሚገባ ይጠቀምባቸዋል። ሆኖም ግን ውሳኔ የሚሰጠው በስሜት ተኮር ሳይሆን በእሴት ተኮር ላይ ተመርኩዞ ነው። ሰዎች በመሆናችን ከእንስሶች የምንለይበት ዋናው ምክንያት የስሜት ተገዢ አለመሆናችን ነው። ራስን መግዛት ለብዙዎች የሕይዎት ዘመን ጉዞ ነው። አንዳንዶች ራስን የመግዛት ሐሳቡ እንዲሳካላቸው ስሜታዊ ሊያደርጋቸው ከሚችል ነገር ራሳቸውን ያገላሉ። ራሳቸውን አግልለውም ከአምላካቸው ጋር ብዙ ጊዜ  ያሳልፋሉ። ትልቁ ነገር ግን ራስን መግዛት ቀላል አለመሆኑን መረዳቱ ነው። ሌላውን ሰው “መግዛት” ይቻል ይሆናል። ለምሳሌ አምባገነን መንግሥታት በሌላው ላይ ነግሠው አገር አስተዳደርን ይላሉ። የሚገርመው ግን ሚሊዮኖችን ገዛን እያሉ ራሳቸውን መግዛት አለመቻላቸው ነው። ራሳቸውን መግዛት ቢችሉ የአምባ ገነንነት ባህሪ አይኖራቸውም ነበር።

ራስን መግዛት ከየትም የሚመጣ  ሳይሆን ከመንፈሳዊነት የሚመነጭ ነው። ለዚህም ነው ሐዋርያው ጳውሎስ ለገላትያ ክርስቲያኖች በላከላቸው መልዕክቱ 5:22 ላይ የመንፈስ ፍሬ ብሎ ካስቀመጣቸው ውስጥ “ራስን መግዛት” አንዱ የሆነው። መንፈሳዊ ሆኖ ፍሬ ማፍራት የግድ ነው። መቸም ገበሬ የዘራውን ለመሰብሰብ በየጊዜው ማሳውን፣ ያፈራውንና ሊያፈራ የጀመረውን እንደሚያይና እንደሚንከባከብ ሁሉ ማንኛውም ሐይማኖተኛ በአንድ በኩል ፍሬ የሚያፈራበትን ነገር ማመቻቸትና አስፈላጊውን መፈጸም ሲያስፈልግ በሌላ በኩል ደግሞ የመንፈሳዊነት ፍሬ ማፍራቱን መከታተል አስፈላጊ ነው። እያወቁ ጥረት (Conscious effort) ማድረግ አስፈላጊ ነው። ከላይ እንደጠቀስኩት አንዳንዶቹ የሕይዎት ዘመን ጥረት ያደርጋሉ። መንፈሳዊ ስንሆን መንፈስን ወይም ዘላለማዊነትን እናስታውሳለን። ዘላለማዊነትን ወይም ሕያውነትን ስንረዳና ሕያው ለመሆን ስንነሳ ደግሞ  የእግዚአብሔር የሆነውን እናደርጋለን እሱንም እንመስላለን። ራሳችን ገዝተን በጊዜያዊ በሚጠፋ ስሜት ሳይሆን ዘላለማዊነትን ተላብሰን ስንኖር በትክክልም ቅዱስ ጳውሎስ እንደሚያስተምረን የዚህ ዓለም ሰዎች ሳንሆን የመንግሥተ ሰማያት ዜጎች እንሆናለን ማለት ነው። ያ ማለት ደስታችን በዚህ አለም ይዞታችን ላይ ወይም በስሜት ሕዋሳቶቻችን ፍላጎት መሟላት ላይ የተመረኮዘ ሳይሆን በራሳችን ላይ በመንገሣችን ይሆናል ማለት ነው።

.... ይቀጥላል

Saturday, November 19, 2011

የሚፈታተነንን ወይም ጊዜ የሚውስድን እንዴት ልንታገሥ እንችላለን?

ከነጋ ዓለማየሁ (November 19, 2011)

እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።” (ዕብራውያን 12: 1-2)
ለመታገሥ ጽኑ ዓላማ ያስፈልጋል። ዓላማ ያላነገበ ሰው ትዕግሥት ከንቱ ይሆንበታል። አንድ የጦር መሪ እና ተራ ተዋጊ ወታደር ትልቅ ልዩነት አላቸው። ወታደሩ ከፊቱ የሚያገኘውን “ጠላት” በተባለው ሁሉ እርምጃ  ለመውሰድ ወይም ለመተኮስ ይቸኩላል የጦር መሪው ደግሞ ከአጠቃላዩ ስኬት ወይም ድል ጋር በማገናኘት ወይም በማገናዘብ መወሰድ ያለበትን እርምጃ ይወስናል። በአብዛኛው ግን የጥቃት እርምጃ ላይ አይቸኩልም፤ መታገሥን ይመርጣል። ይህም የሚሆንበት እያንዳንዷ  እርምጃ ከዋናው ለመጨረሻው ድል ታቀርበናለች ወይስ ታርቀናለች ብሎ በማሰብ ነው። የጠላት ኃይል ምንም እንኳ ጥቃትን ቢያደርስም ከመጨረሻው የግብ አቅጣጫ ጋር በማገናዘብ መታገሥን ይመርጣል። ይህ የሚሆነው መዳረሻውን የሚያውቅ መሪ ሲሆንና እንደሚደርስም ሲያምን ነው።  

በመግቢያ ላይ የተጠቀሱት ከዕብራውያን 12:1-2 የተወሰዱት ጥቅሶች የሚያመለክቱት ይህንን ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያንን ሁሉ የደረሰበትን መከራ የቻለበትና ነውር የናቀበት ዋናው ምክንያት በእግዚአብሔር ዙፋን በቀኝ እንደሚቀመጥ በማወቁ ነው። የመከራው ብዛት የሰው ልጆች የፈጸሙትን ሐጢያት የሚያሳይ ሲሆን የእርሱ መታገሥ ግን ለማዳን የመጣ በመሆኑና ወደነበረበት ቦታ በክብር መመለስ ስላለበት የሆነ ነው።

በዛሬ ዘመን መታገሥ ሞኝነት ይመስላል። ሞኞችም የጠፉ ይመስላሉ። ሰዎች መታገስ እያቃተንም ብዙ ቁምነገር ያላቸው ነገሮች ቤተሰብንም ሆነ ማህበረሰብን ብሎም አገርን ሊጠቅሙ የሚችሉ ጉዳዮች ሲበላሹ እናያለን። ይህም ሊሆን የቻለበት ከአሰባሰበን ጉዳይ ይልቅ ወይም ከትልቁ ዓላማ ይልቅ እያንዳንዳችን ተልቀን እንገኝና የተለያዩ  አመለካከቶችን ማስተናገድ ባለመቻላችን ትንንሽ ውጣ ውረዶችን መታገሥ ባለመቻላችን ዓላማችን ሳናሳካ እንበታተናለን።

ቤተሰብ ለምን ተመሠረተ? እኔስ ለምን ቤተሰብ መሠረትኩ? ዓላማው ምንድን ነው? እነዚህን ጥያቄዎች በአግባቡ የመለሰ ቤተሰብ ተፋቅሮ፣ ተከባብሮና ተግባብቶ የመኖር እድሉ ሰፊ ነው። ቤተሰብ የተመሠረተበት ዓላማ የጊዜ ገደብ የለውም። የእድሜ ልክ ዓላማ ነው። ያ በመሆኑ በአንድ ጣራ ሥር የሚኖሩ ሰዎች አንድ የሚያደርጋቸው የቤቱ ጣራ ሳይሆን መሆን ያለበት ያገናኛቸው ዓላማ  ነው። ዓላማ አንድ ካደረጋቸው የቤቱ ግድግዳም ሆነ ጣራ ባይኖር በአንድ ላይ ተያይዘው ይገኛሉ። በዛሬው ዓለም የቤቱ ጣሪያ አስገድዶ በአንድ ላይ የሚያኖራቸው ቤተሰቦች ቁጥር በጣም ብዙ ነው። አንድንዶቹ ቤታቸውም ሰፊ በመሆኑና ብዙ ክፍሎች ስለሚኖሩት ምንም እንኳ ለውጭ ሰው በአንድ ቤት በመኖራቸው በአንድ ላይ የሚኖሩ ቢመስሉም መኝታ ለይተው ይኖራሉ። እንግዲህ በአንድ ጣራ ሥር የተለያዬ ክፍል ማለት ነው። ይህን ምን አመጣው ብንል መጀመሪያውኑ አንድ ጣራ  ሥር የመጡበትና ምክንያትና ዓላም ረስተውታል ማለት ነው።

ክርስቲያን ለሆነ ቤተሰብ እግዚአብሔር የመሠረተው ተቋም በመሆኑ ያንን የእግዚአብሔርን ዓላማ እያሰቡ በትዕግሥት ይኖራሉ። ትዕግሥት የሚያስፈልገውም አንዳንዴ ለሚፈጠር የሕይወት ውጣ ውረድ ነው። ውጣ ውረዱ ያለና የነበረ  ወደ ፊትም የሚኖር መሆኑን  ይረዳሉ። የማይፈተን እድገት የለውም። ውጣ ውረዱ ወደ ተሻለ ደረጃ ለመድረስ አስፈላጊ ነገር መሆኑን ይረዳሉ። ጎበዝ ተማሪ ፈተና  አይፈራም። ለምን ቢባል ፈታናውን አልፎ  ወደሚቀጥለው ክፍል እንደሚያልፍ ስለሚገነዘብ ነው። ስለዚህ ችግርን መታገሥ፣ እለታዊ ስሜትን ሳይሆን ዘላቂ ዓላማን መሠረት በማድረግ ውሳኔ  መስጠት ለጥሩ ውጤት ያበቃል።  

አገርን እንመራለን ብለው የሚደረጁትም ብዙ ጊዜ ሲፈርሱ አይተናል። እኔ በዚህ ውስጥ ለነበሩ የምጠይቀው ጥያቄ ቢኖር “ለምን ጀመራችሁ ለምንስ ታፈርሳላችሁ?” መቸም ይብዙዎችን መልስ ስንሰማው የተለመደው እጣትን በሌላው ላይ መቀሰር ነው። እጣት የሚቀሰርበትንስ እንዴት መታገሥ አልቻሉም? እኔ እንደማስበው አንድ ላይ እንዲመጡ ያደረጋችውን ትልቁን ዓላማ ካልረሱት በስተቀር መታገሥ አይቸግራቸውም። ዋናው ዓላማ ከተረሳ ግን ዓላማውን ለማስፈጸም የሚቀረጸው ስትራተጂ የአለመግባባት ምንጭ ይሆንና ዋናው ነገር ተረስቶ ይቀራል። ዋናው ዓላማ ካልተረሳ  ግን ማንኛውም ዓላማውን ለማሳካት የሚመጣ ሐሳብ ሁሉ ልንቀበለው የግድ ይሆናል። ማንም ያመንጨው ማንም ጥያቄ ውስጥ የሚገባ መሆን የለበትም። ዋናው ነገር ከግባችን ለመድረስ ይረዳናል ወይስ አይረዳንም ነው መሆን ያለበት።

ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ ረጂም ጊዜ ይወስዳል። ይህ ረጂም ጊዜ የሚወስድ ነገር በዋናነት ትዕግሥትን ይፈልጋል። እስራኤላውያን ከግብፅ ምድር ወጥተው ወደ  ቃል ኪዳኗ መሬት ለመግባት 40 ዓመታት ተጉዘዋል። በዚህ ትዕግሥት አስጨራሺ ጉዞ ብዙዎቹ አልደረሱም። የታገሱትና እንገባለን ብለው ያመኑት ግን ደርሰዋል። ትዕግሥት ዓላማን ማወቅና ይሆናል ብሎ ማመንን ይጠይቃልና ነው። ስለዚህ መታገሥ የሚያስቸለን ዋናው ነገር የምንታገሠው ለምንድን እንደሆነ  ማወቁ ነው።

... ይቀጥላል

Thursday, November 10, 2011

ትዕግሥት ለምን ያስፈልጋል?

በዘመናችን አንድን ነገር ለማግኘት በችኮላ መፈለግ ወይም በፍጥነት መድረስ ወይም መፈጸም አለበት የሚል አስተሳሰብ በሰፊው ይንጸባረቃል። ልጆች አንድ ነገር ጠይቀው ወዲያውኑ ካላገኙ የቤቱን ሰላም ይፈታተናሉ። ልጆች ብቻም ሳይሆኑ ታላላቆችም ቢሆን አንድን ነገር በመታገሥ መጠበቅ አስቸጋሪ ሆኗል። እውነታው ግን ሁሉም ነገር የሁነታ ጊዜ አለው። የሰው ልጅ ጽንስ ተረግዞ ልጅ ሆኖ እስከሚወለድ የ9 ወር ጊዜ ያስፈልጋል። በመሆኑም አንድ ሰው ተነስቶ  ልጅ እፈልጋለሁና አሁንኑ ይድረስ ብሎ ማሰብ አይችልም ካሰበም የጤና ችግር አለባቸው ከሚባሉ ሰዎች አንዱ ይሆናል ማለት ነው። መስከረም አልቆ ሌላ መስከረም እስኪመጣ 11 ወራት መቆጠር አለበት። ምግብም የመብሰያ ጊዜውን ጠብቆ መብሰል አለበት። ያ ሊሆን ካልቻለ ያለጊዜው ሳይበስል የተበላ ምግብ ለጤና ተስማሚም አይሆንም።  
        በችኮላ መፍትሔ ተብሎ የተወሰደ ነገር ሁሉ በአብዛኛው ትክክለኛ መፍትሔ አይደለም። አባቶቻችን ሲተርቱ “የነቶሎ ቶሎ ቤት ግድግዳው ሰንበሌጥ” ይላሉ። በመሆኑም ትዕግሥት የአንድን ነገር የሁነታ ጊዜ እንዳለው በመረዳት መጠበቅ የግድ ይሆናል። ጥበቃው ታዲያ እምነትም ያስፈልገዋል። ይሆናል ብሎ ለመሆኑ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ማመቻቸት አስፈላጊ ነው። ትዕግሥትን በሚገባ ተረድተን ስንታገስ በየጊዜው የሚገጥመን ነገር ስሜትን የሚጎዳ አይሆንም። ያሰብነው ነገር ሳይሳካ ቢቀር ወይም ካሰብነው ጊዜ ውጭ ቢራዘም አሁንም በጠቢቡ ሰለሞን አድሮ “ለሁሉም ጊዜ አለው” ያለንን እግዚአብሔርን እናስታውሳለን ተስፋም እናደርጋለን። የትዕግሥት አስፈላጊነትም ይህንን እውነታ እንድንረዳ ነው። አንድ ሰው አንድ የማይፈለግ ጸባይ ቢኖረው ያንን ጸባዩን ለመቀየር ትልቅ ትዕግሥት ያስፈልጋል። በመጀመሪያ ደረጃ ያንን መልካም ያልሆነውን ጸባዩን ለመያዝ ጊዜ ወስዶበታል። ታዲያ ጊዜ ወስዶ ያጠራቀመውን ነገር በአንድ አፍታ ሊቀይረው አይችልም። እሱ እራሱም ሆነ በዙሪያው የሚገኙት ሊታገሱ ይገባል።
እግዚአብሔርን ተስፋ አድረገው የተንቀሳቀሱ ሁሉ ታላቅ ትዕግሥት አሳይተዋል። እስራኤላውያን ከግብፅ ምድር በባርነት ከሚገዙበት ወጥተው ወደ ቃል ኪዳኗ መሬት ለመግባት 40 ዓመታት ወስዶባቸዋል። በዚህ በእስራኤላውያን የነፃነት ጉዞ የእግዚአብሔር እጅ ሆኖ ዋና ተዋናይ የነበረው ነቢዩ አባታችን ሙሴ ብዙ ነገሮች የገጠሙት ቢሆንም ሰዎቹን በትዕግሥት አስተዳድሯል። ምንም እንኳን ወደ ቃልኪዳኗ መሬት መግባት ባይችልም የነፃነት ጉዞው አውራ ተዋናይ በመሆን ይታወቃል።
እዮብ ከአብራኩ የወጡትን ልጆችና በዓለም ያፈራቸውን ህብቱንና ንብረቱን ሲያጣ ወደነበረበት ክብሩና የበለጠም ሀብት እንዲያገኝ ያደረገው ትዕግሥት የተባለው የመንፈስ ፍሬ ነው። ባለቤቱም ሆኑ የቅርብ ሰዎቹ የደረሰበት ነገር ከባድ መሆኑን ነግረው እግዚአብሔርን ማምለኩን እንዲያቆም ለማሳመን ሲሞክሩ በእምቢተኝነት እንዲቆይ ያደረገው ትዕግሥት ነው። አሁን ባለንበት ዘመንም መታገሥ የቻለ ረጅም መንገድ መሄድን ይመርጣል የተሻለ ቦታም ይደርሳል። ረጅም መንገድ የሚሄዱም በመንገድ ብዙ ችግሮች ይገጥሙአቸዋል። ሆኖም ግን በትዕግሥት ካሳለፉት ቀደም ሲል ካሰቡት መድረሻቸው ሲደርሱ ፍሬው ያስደስታቸዋል። የታመመ ሰው እድናለሁ ወይም ወደ አምላኬ እሄዳለሁ የሚለውን በማመን ታጋሽ ከሆነ በህመሙ አይሰቃይም። እንዲያውም በአካባብው የሉትን ሰዎች የሚያረጋጋ ይሆናል።

... ይቀጥላል

Wednesday, November 9, 2011

ትዕግሥት


ት የውን ቃል ወይም ጽንሰ ሃሳብ በአብዛኛው የመንጠቀምበት ስሜታችን የሚፈታተኑ ነገሮችን ችሎ ከማለፍ ጋር በተያያዘ ነው። ለዚህም በተለምዶ

“መቻል ምን ይከፋል
ሆድ ከአገር ይሰፋል” ይባላል።

አንድን ነገር ታግሠን በማሳለፋችንም በአብዛኛው ደስተኞች እንሆናለን። ይህ አይነቱ መታገሥ በወቅቱ የባሰ ችግር እንዳይገጥም የሚጠቅም ሲሆን በችግሩ ዙሪያ ግን ዘለቄታዊ መፍትሄ ላያመጣ ይችላል። ት ስሜትን አምቆ መያዝ ሳይሆን የምንፈልገው ነገር ቀና በሆነ አስተሳሰብ ይሆናል ብሎ መጠበቅን ይመለከታል። ት ውጤቱ ብቻ ሳይሆን በትክክል ከታገን ሂደቱም አስደሳች ነው። በውስጥ “አንጀትን እያሳረሩ” ስለትት ማውራት ትዕግሥትን በሚገባ አለመረዳትን ከማመላከቱም በላይ ጎጂነቱ ስለሚያመዝን ሰዎች መታገስን እንደሞኝነት ሊቆጥሩት
ትዕግሥት ምንድን ነው?
በህይዎታችን መታገን የሚፈልጉ ብዙ ገጠመኞች አሉ። በዚህ ውስብስብ በሆነ ዓለም ውስጥ መታገሥ ወይም አለመታገሥ ጉልህ አስተዋጽኦ አላቸው። አንዳንዴ ት ሳይሆን ፍጥነት የሚያስፈልጋቸው ነገሮች አሉ። የአንድ ደቂቃ መዘግየት ይኸ ነው የማይባል የሕይዎት ዘመን ዕድል ሊያሳጣ ይችላል። በተቃራኒው ደግሞ ለሴኮንዶች መታገሥ አለመቻል ለህልፈተ ሕይዎት ያደርሳል። ለምሳሌ ያህል መኪና የሚነዳ ሰው መታገሥ ባለመቻሉ ከፍተኛ አደጋ እንዲደርስ ያደርጋል። ይህ እንግዲህ ን ከጊዜ ጋር ስናየው የመታገሡ ሁኔታ ሳይሆን ጊዜ ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ ነው የምናየው። በአንድበኩል በመዘግየት ሊቀርብን የሚችል አጋጣሚ በሌላ በኩል ደግሞ በመቸኮል የሚደርስብን ጉዳት። የተረጋጋ ሕይዎት ያለው በብርሃን የሚኖር ይህንን መለየት ስለማይቸገር ሁለቱንም እንደሁኔታቸው ያከናውናል።
ይህንን ጽንሰ ሐሳብ ማለትም ከጊዜ ጋር የተያያዘውን ያመጣሁበት ምክንያት አንባቢዎቼ “መታገሥ ድርጊት አለመፈጸም ነው” ከሚለው ጋር እንዳያያይዙት ከመፈለግ ነው። እየሱስ ክርስቶስ ያንን ሁሉ መከራ በ ያሳለፈበት ምክንያት ውጤቱን በማወቁ ነው። ውጤቱም ለሰው ልጆች ድኅነትን ማምጣት፣ የእግዚአብሔርን ማንነት ማሳየት - ሙቶ ሌሎችን በማዳን። እንደዚህ አይነቱ ከፍተኛ ኃይል አለው። መታገሥ የሚያስፈልጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ። ለምሳሌ ያህል፦
·         የቤተሰብ ግንኙነት የሰመረ ለመሆን
·         በሥራ ቦታ ከሥራ ባልደረቦች ጋር ያለ ግንኙነት አለማማር
·         ያለንበት የኢኮኖሚ ሁኔታ ዝቅተኝነት
·         በራሳችንም ሆነ  በምንወዳቸው ላይ የደረሰ የጤና ችግር
·         የምንወዳቸው ሰዎች ያሉበት ሁኔታ መልካም አለመሆንና የመሳሰሉት
·         በዓለም ላይ ያሉ ፍትሀዊ ያልሆኑ አሰራሮች
ባለት ዘመን የሚታዩ ክስተቶች ናቸው። እነዚህ ክስተቶችም እልህ አስጨራሾችና ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ይታመናል። ሰዎች የችግራቸውን መፍትሔ የማግኛ ጊዜ ለማሳጠር መታገስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይህንን ስል የችግሩ ባለቤቶች እጃቸውንና እግራቸውን አጣጥፈው ቁጭ ይላሉ ማለት አይደለም። ማድረግ ያለባቸውን ነገር መጫዎት ያለባቸውን ጨዋታ ማለትም የራሳቸውን ድርሻ መወጣት የግድ ነው። መታገስ ማለትም ውጤቱን ከመጠበቅ አንጻር እንጂ የራስን ድርሻ ለመፈጸም መታገስ ቦታ የለውም።
አንዳንድ ጊዜ ችግር ሲደርስ ከችግሩ በመሸሽ መፍትሔ ያገኘን ሊመስለን ይችላል። ሆኖም ግን ዘለቄታዊ መፍትሔ የምናገኘው ችግሩን በመግጠም ነው። ችግሩ በደረሰ ጊዜም ከችግሩ መሸሽ ሳይሆን በ መፍትሔ መፈለግ ጠቃሚ ነው። ጠቢቡ ሰለሞን የን ኃይል ሲገልጽትዕግሥት ታላቁን ኃጢአት ጸጥ ያደርጋልና የገዢ ቍጣ የተነሣብህ እንደ ሆነ ስፍራህን አትልቀቅ። (መክብብ 10:4) በበላይ አካል ቁጣ ተደናግጦ ቦታን መልቀቅ እንደማያስፈልግና በኃጢአት ላይ ምን ያህል ሃያል ስልጣን እንዳለው ያስረዳናል። ቦታውን ከለቀቅን የምናስበውን ነገር ተተነዋልና ሊደግፉን የሚያስቡ ሰዎች ካሉም ሀሳባችን መተዋችንን (መሸሻችንን) በማየት ሊዘረጉ ያሰቡትን የትብብር እጅ ይሰበስባሉ።
ከት ጋር ሁልጊዜ አብሮ የሚሄደው ቀና አስተሰሰብ ነው። ስንታገሥ ውጤቱ መልካም ይሆናል በሚል አስተሳሰብና ለቀናው ነገር መምጣት የበኩላችን አስተዋጽኦ በማድረግ መሆን አለበት። ጠማማው ይቃናል፣ የጎደለው ይሞላል፣ የተጣላው ይታረቃል፣ የታመመው ይድናል፣ የወደቀው ይነሳል፣ የተጣላው ይታረቃል፣ ያበላሸው ያስተካክላል፣ ያልታየው ያያል፣ የተደበቀው ይገለጻል፣ የጠፋው ይገኛል፣ ያጣው ያገኛል፣ የተሳሳተው ይመለሳል እና የመሳሰሉትን ቀና አስተሳሰቦች በማሰብና ለተግባራዊነታቸውም ሌት ተቀን መሥራትን ይፈልጋል። ትዕግሥት እንቅስቃሴ አልባ ሳይሆን በይሁንታዊ ቀና አስተሳሰብ እየተመራ ተግባራዊ እንቅስቃሴን ይፈልጋል።   
በቅዱስ መጽሐፍ እንደምናየው ነቢያት ከፍተኛ ችግር የደረሰባቸው ቢሆንም የሚጠብቁትን ነገር ይሆናል ብለው አምነው ይህንኑም በትዕግሥት ጠብቀዋል። ይህንንም ያዕቆብ ሲገልጽ እንዲህ ይላል “ወንድሞች ሆይ፥ የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ።” (ያዕቆብ 5:10) በያዕቆብ መልዕክት ምዕራፍ 1:2-4 እንደተጠቀሰው በእምነታችን ላይ ለሚመጣው ፈተና ትዕግሥት ሥራውን እንዲሠራ ሁኔታውም ሲከሰት ደስ ሊለን እንደሚገባ ያስረዳል። ፈተና በቀና ለሚመለከቱትና ለተዘጋጁ ተማሪዎች ከክፍል ወደ ክፍል እንደሚያሳልፍ ሁሉ በሕይዎትም የሚገጥም ችግር ወደተሻለ ደረጃ እንደሚያሸጋግር እሙን ነው። የፈጠራ ሥራዎች የችግር መፍትሄዎች ናቸው። “ችግር ብልሀትን ይፈጥራል” እንደሚባለው።   
መከራን በመታገስ ዋነኛ ስፍራ ከሚይዙት ውስጥ ኢዮብ አንዱና ታላቁ ነው። ኢዮብም መታገሱን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርም እንደፈጸመለትም መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል። “እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደ ፈጸመለት አይታችኋል፤ ጌታ እጅግ የሚምር የሚራራም ነውና።” (ያዕቆብ 5:11) የእግዚአብሔር ለሚታገሡት ምህረቱ እምን ነው።
ብዙ ፈታኝ ነገሮች በሩቅም ተፈጽመው ተመዝግበው ያሉም ሆነ አሁን በቅርብ ዘመን የተከሰቱት ትዕግሥትን የጠየቁ ነገሮች በአብዛኛው ረጂም ጊዜን ወስደዋል። እስራኤላውያን በነቢዩ ሙሴ እየተመሩ ከግብጽ ወጥተው ወደ ቃል ኪዳን መሬት ሲሄዱ ጉዞው እልህ አስጨራሽ ከመሆኑም በላይ ብዙ ዓመታትን (40 ዓመታት) ወስዷል። ብዙዎችም ወገኖቻቸው እንደሚደርሱ ከማመን በስተቀር ባይናቸው ለማየት አልበቁም። ተመሳሳይነት ያላቸው ከዚያ ቀረብ ያሉ ብዙ ክስተቶችንም መጥቀስ ይቻላል። ይህንንም ለአንባቢዎቸ እተወዋለሁ።
በእግዚአብሔር ለሚያምኑና መንፈሳውያን ለሆኑ ሕይዎታቸውን ለጌታ ለእየሱስ ክርስቶስ ለሰጡ የመንፈስን ፍሬዎች ማፍራት እንዳለብን ሐዋርያው ጳውሎስ ሲያስተምረን ፍሬዎች ብሎ ከገለጻቸው ውስጥ “ትዕግሥት” አንዱ ነው።  እግዚአብሔርም ለሰው ልጆች በአካል የተገለጸ ባይሆንም መልካም እንደሚያስብ በነቢዩ ኤርሚያስ “ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።” (ኤር 29:11) ሲል ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል። መልካሙንም ነገር ሁሉ በጊዜው ያደርጋል ብሎ በእምነትና በትዕግሥት መጠበቅ መንፈሳዊ ፍሬ የማፍራት ምልክት ነው። 

... በሚቀጥለው ትዕግሥት ለምን ያስፈልጋል? እና የሚፈታተነንን ወይም ጊዜ የሚውስድን  ነገር እንዴት ልንታገእንችላለን? በሚሉት ጉዳዮች ላይ ያለኝን ሐሳብ አቀርባለሁ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ነጋ ዓለማየሁ

Finding Hope in a Hopless environment

Finding hope in a hopless environment
It is true that in the world of today, it is very easy to lose hope because of the broken things that we see here and there. It seems that no body has control over anything. How can I be certain about my future? How can I fix things aroud me? I see so many things falling apart. “What a curse!” could be the words that one sees in the back of his mind.
This happens when you pass on the remote control to another person. Expecting others to fix the environment around me and make me feel good is like giving them my remote control. They can turn me OFF or ON. That is like I am in their mercy.
I must take responsibility to whatever happens around me. When I am responsible I am able to respond (response-able) to any stimulus. It is my response to whatever happens around me that causes my emotional status. I must make a choice that brings benefit to myself as well as others. I may be in a situation where people regularly argue and fight, I may be in a situation where someone gets mad at me, I may be in a situation where material needs are not fulfilled, etc. Now the question is “How do I respond to such situations?” Definitely, the common thing to do is respond accordingly. If someone screams at you scream back; if members of the family are arguing get involved in the conversation and shout at them. Would this help? No. It is like turning the lights off during night time. 
Whenever there is misunderstanding and problems it is said to be darkness everywhere. It is important that a candle light during night time helps a great deal. I can become the candle light and let those who argue to see each other rather than letting them step on each other’s toe in the darkness. That brings benefit to the self and others. God is the light. Whenever He is invited there won’t be any darkness. Darkness and light can’t live together. That is why we have to keep God in our hearts. You become the little candle that gets its energy from the supreme eternal light, God. Remember you can be a source of inspiration for people around you. People will always see those who are stable emotionally at the time of crisis.
Take a break from the mundane life and reflect on the characters of GOD. Pray and get the energy that you need from time to time. Don’t be in a rush to fix problems that existed for long time. It took the Israelites 40 years to get to the Promised Land even with the direct supervision of the Almighty God. Moses didn’t make it to the Promised Land. Patience in faith is important. That means believing that things around me will change to the better and working towards achieving it. 
... will continue. 


Nega Alemayehu